እምነታችን
ሁሉን በፈጠረ አንድ አምላክ በሚሆን በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ሰማይና ምድርን የፈጠረ የሚታየውንና የማይታየውን ፣ ዓለም ሳይፈጠር ከርሱ ጋር በነበረ አንድ የአብ ልጅ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን። ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ እውነተኛ አምላክ የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ በባሕርዩ ከአብ ጋር የሚስተካከል ሁሉ በእርሱ የሆነ በሰማይም ካለው በምድርም ካለው ያለርሱ ምንም ምን የሆነ የለም። ስለኛ ስለሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፣ ደግሞ ስለኛ ተሰቀለ። በጴንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን እርሱ መከራን ተቀበለ ፤ ሞተ፣ ተቀበረ በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተሰሣ ፤ በቅዱሳት መጻህፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደሰማይ ዐረገ ፣ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ፣ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ በምስጋና ይመጣል ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም። በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እርሱ ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረፀ ከአብና ከወልድ ጋራ በአንድነት እንሰግድለታለን ፣ እናመሰግነዋለን ፤ እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረ ነው። ከሁሉም በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ክብርት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን። ኃጢአት በሚሠረይባት በአንዲት ጥምቀትም እናምናለን፤ የሙታንንም መነሣት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ።

SERVICES

Baptism

ክርስትና/ጥምቀት

በዕለቱ የ 40 እና 80 የ ልጆች የጥምቀት አገልግሎት

Sunday School

የሰንበት ት/ቤት

ለልጆች ኦርቶዶክሳዊ አስተዳደግና ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር በተጠናከረ መልኩ ይሰጣል።

Sunday Prayer

ቅዳሴ

ዘወትር እሁድ የ በዓላት ዕለት የቅዳሴ የወንጌል የዝማሬ የጥምቀት አገልግሎት

Public Teaching

ፍትሃ ጸሎት

በዕለቱ የ 40 የ ሙት ዓመት የጸሎት ፍትሐት አገልግሎት


Events | መጪ በዓላት

ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና::

ሉቃስ 6÷38
የቤተክርስቲያናችን አባል ይሁኑ
የደብረ ምጥማቅ ዳግማዊ ፃድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን አመሰራርት
ደብረ ምጥማቅ ዳግማዊት ፃድቃኔ ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሰቲያን በእግዚአብሔር ፈቃድ ና በብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ፈቃድ 2018 ዓ/ም ተመሰረተች። ለሦስት ተከታታይ ዓመታት ቤ/ክ ተከራይተን ለምዕመንናን ሰፊ አገልግሎት ሲሰጥ ከቆየ በኋላ 2020 ሐምሌ 24 በተመሰረተ በ3ኛ ዓመት 14549 Town Center Rd Woodbridge va 22192 እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ቤተክርስቲያን ለመገዛት ተችሏል አሁን ለምዕመናን 24 ሰዓት ዘውትር ክፍት ሆኖ አግልግሎት ምዕመናን ንስሀ ገብተው የጌታን ስጋ ና ደም ይቀባላሉ ልጆች ሀይማኖታቸውን ጠንቅቀው እንዲውቁ የሃይማኖት ትምህርትና የግዕዝ የአማርኛ ትምህት እየተሰጠ በ3 ቀሳውስት በ 9 ዲያቆናት እግዚአብሔር እየተመሰገነ የነፍስ ምግብ እየተሰጠበት ይገኛል።ደብረ ምጥማቅ ዳግማዊት ፃድቃኔ ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርሰቲያን በአሜሪካ ፌደራል መንግሥት (501) (ሲ) (3) መሠረት የተቋቋመ በቃለ ዓዋዲ በሰበካ ጉባኤ የቤተ ክርስቲያን (ዋና አስተዳዳሪ) ካህን ትመራለች።
Debre Matmak Dagmawit Tsadkane Mariam Ethiopian Orthodox Tewahedo Church was established by the will of God and the permission of His Holiness Abune Fanuel in 2018. After renting the church for three consecutive years and providing a wide range of services to parishioners, we now have moved to our building 13327 Woodbridge St, Woodbridge, VA 22191, in the third year of its founding, on July 24, 2020, according to God’s will. Debre Mitmak Dagmawi Tsadikane St. Mary Ethiopian Orthodox Tewahedo Church is based in Woodbridge VA. The church was established in March 2018 and serves Woodbridge and surrounding DMV area.

ፍልሰታ ለማርያም መርሃ ግብር በጻድቃኔ ማርያም ቤ/ክ